አስፓየር ማይክሮ ፋይናንስ አክሲዮን ማኅበር ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ጥር 2017 ዓ/ም የመስራቾች ፈቃድ በመውሰድ ለሕዝብ ይፋ ባልሆነ (Non-public ) የአክሲዮን ሽያጭ መሰረት በተፈረመና በተከፈለ የማይክሮ ፋይናንስ ለማቋቋም በተፈቀደው አነስተኛ የካፒታል መጠን ብር 75 ሚሊዮን ብር የመስራቾች ጉባኤውን ጥቅምት 15/2018 ዓ/ም በሂልተን ሆቴል አካሂዷል::
በጉባኤው ላይ ቅድመ ጉባኤ የተከናዎኑ ተግባራት፣ የውጪ ኦዲት ሪፖርት፣ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት በመምረጥና በሌሎች አጀንዳዎችች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል::
አስፓየር ማይክሮ ፋይናንስ አስፈላጊ የሕግ ሂደቶችን በማጠናቀቅ የፋይናንስ ኢንደስትሪውን በቅርቡ እንደሚቀላቀል ይጠበቃል::
